XtGem Forum catalog
free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

App full proxy-5.php 22

ውድ ሙስሊም እህት ወንድሞቼ ጊዜው ሳይጨልምብን የሞትን ቅጣት ከመቅመሳችን በፊት ወደ አሏህ እንመለስ

App full proxy-5.php 23

አሏህ ሱ.ወ.ተ የሰው ልጆችን የፈጠረበትን አላማ ሲገልፅ በቁርአን እንዲህ ይላል:-

«የሰው ልጆችንም ሆነ ጅኖችን አልፈጠርኩዋቸውም እኔን ሊገዙኝ ቢሆን እንጂ።»

እኛ የሰው ልጆች የተፈጠርንበትን አላማ ረስተን አለማዊ በሆኑ ነገሮች ተነድፈን ፤ አሂራን ረስተን ዱንያን ለማሳመር ከታች ከላይ ማለታችነን ቀጥለናል። ይህ ምን ያህል ልቦቻችን በድንቁርና ፅልመት እንደተሸፈኑ የሚያመላክት ነው።

እስኪ በልቦቻችን ውስጥ ያለውን እውነታ በጥያቄ መልክ እንመልከት።

√ ቁርአንን በቀን ቢያንስ ሶስት ጊዜ የምንቀራ ምን ያህሎቻችነን?

√ ሶላታችነን በተደነገጉት የሶላት ሰዓት የምንሰግድ ፣ ኢስላማዊ እውቀትን ለመሻት የምንጣጣርስ ስንቶቻችን እንሆን?

√ ስለዲናችን ወቅታዊ ጉዳዮችስ ቁጭ ብለን የምንወያይ ስንቶቻችን እንሆን?

√ አይደለም ስለወቅታዊ ጉዳዮቻችን ቁጭ ብለን መወያየት ይቅርና ሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጋር ሰላምታን መለዋወጥ እረፍት እየሆነብን አይደለምን? እንደ ሙስሊምነታችን ከኛ የሚጠበቁብንን ነገሮች የምንሰራስ ስንቶቻችን እንሆን?

√ ወላጆቻችነን በቅን መንፈስ እያገለገልን ያለን ፣ ኢስላማዊ ባህሪያትን የተላበስን ፣ አሏህ ከከለከለው ነገር የተከለከልን ፣ የአሏህን ቅጣት ፈርተን ተውበት እያደረግን ስቅስቅ ብለን የምናለቅስ እና ሂወታችነን በቁርአንና በረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ሱና እየመራን ያለን ስንቶቻችን እንሆን?


ሶላት

5003058 f84567a775 3551280 680712068607679 834699509 n

=<({አል-ቁርአን 29:45})>=

إِنَّ الصَّلَاةَ تَنْهَى عَنِ الْفَحْشَاء وَالْمُنكَرِ

ሶላት ከመጥፎና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለች።

ሶላት ልብን ብርሃን የምታድርግ ፣ የስኬት ሚስጥር ፣ የጀነት ቁልፍና ከአሏህ ጋር ያለንን ትስስር የምናጠነክርበት ፣ የአሏህን ውዴታ የምናገኝበት ፣ ለአሏህ ትእዛዝ ያለንን ታዛዥነት ፣ ባርነታችንንና ለማኝነታችነን የምንገልፅባት ብቸኛዋ የኢባዳ ተግባር ናት። ሶላት በጭንቀት ጊዜ እረፍትን ሰጭ ፣ ለችግሮች መፍትሄና የሃጥያቶች ማበሻ ናት።


483024 558942324131493 320607529 n

ዛሬ ዛሬ ሶላትን መስገድ ፣ ቁርአን መቅራት ፣ ሂጃብን መልበስ የትርፍ ጊዜ ስራ እየሆነ መጥቷል። በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ይህንን እውነታ ለማረጋገጥ በተለያዩ ማህበራዊ ድህረገፆች ፣ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና በየሰፈሮቻችን ባሉ መስጅዶች ያለውን አህዋል መመልከት በቂ ነው።

ሶላት አንዱ የኢስላም ምሰሶ እንደሆነ ይታወቃል። ሶላትን አለመስገድ አንዱን የኢስላም ምሰሶን እንደ መናድ ነው።
ለሶላታችን ትኩረት ልንሰጥ ይገባል። አትኩሮት አይደለም ለሶላት በውዱእ ወቅት እንኴ ትኩረት ሰጥተን ተረከዛችነን በደንብ እንድናጥብ ፣ እያንዳንዷን ክፍል እንድናዳርስና ተረከዛችንንም ከጀሃነም እሳት እንድንጠብቅ ከሁሉም ነገር በላይ ተወዳጅ የሆኑት ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) አዘውናል።

ጥራዝ 1,መጽሐፍ 3,የሐ.ቁጥር 57

አብዱሏህ ቢን አምር እንደተረከው
አንዴ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በጉዞ ወቅት ከኋላችን ቀርተው ነበር። ለሶላት ውዱእ እያደረግን እያለ ተቀላቀሉን። በእርጥብ እጃችነም እግሮቻችነን እያበስን ነበር። እናም ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ሁለቴ እና ሶስቴ ተረከዛችሁን ከጀሃነም እሳት ጠብቁ አሉ።


App full proxy-5.php 25

ከሶላት እንድንርቅ ከሚያደርጉ ነገሮች.....

App full proxy-5.php 24

• ቸልተኝነት

• ነገን እቶብታለሁ በማለት ሃጥያትን መዳፈር

• ከቁርአንና ከሐዲስ መራቅ

• ትኩረትን አለማዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ብቻ ማድረግ

• ማህበራዊ ድህረገፆችን አዘውትሮ መጠቀም

• መጥፎ ጓደኛ

• እውቀት አለመኖር

• የአሏህ ፍራቻ በልባችን ውስጥ አለመኖር

• የቀልብ መድረቅ

• በኢስላማዊ ባህሪ ተኮትኩቶ አለማደግ

• የአስተሳሰብ ዝንፈት

• ጌሞችን አዘውትሮ መመልከትና መጫዎት

• የሰይጣንን መንገድ መከተል

በሰላታችን ጠንካራ ለመሆን ከሶላታችን እንድንርቅ ያደረጉንን ነገሮች ልናስወግድ ይገባል።


App full proxy-5.php 26

በዙርያችን ከሶላት የራቀ ሰው ካለ የሚከተሉትን ነገሮች ልናደርግለት እንሞክር

App full proxy-5.php 27

۵ ዳእዋ ማድረግ

۵ ሰውየው በራሱ ከሶላት እንዲርቅ ያደረጉትን ነገሮች ነቅሶ እንዲያወጣ ማገዝ።

۵ ተውበት አድርጎ ወደ ሶላት እንዲመለስ ግፊት ማድረግ

-አብሮን እንዲሰግድ ማበረታታት

-ማስታወስ

- ለዚህ ሰው ሁሌም ከጎኑ በመሆን የሚቸግሩት ነገሮች ካሉ ማገዝ

۵ የአሏህ ፍራቻ በልባችን ውስጥ እንዲኖር ማድረግ

- የሶላትን ምንዳ ማስታወስ

- ሶላትን የመተው ቅጣት ምን እንደሆነና የፍርዱን ቀን መከራ ማስተንተን

- የዚች አለም ውስንነት በጥልቅ መረዳት

۵ እውቀትን መሻት

۵ ዱአንና ኢስቲግፋርን ማብዛት

۵ የመልካም ስብእና ባለቤት መሆን

۵ ከመጥፎ ጓደኛ መራቅ

۵ ታናናሽ ወንድሞቻችነን ፣ እህቶቻችንና ልጆቻችነን በኢስላማዊ ባህሪያት ኮትኩተን ማሳደግ

=> ከማንኛውም ነገር በላይ ለሶላት ቅድሚያ እንስጥ

'~'-.,__,.-'~'
_,.-'~''~'-.,_


App full proxy-3 90
1588

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ